ይህ የመሬት ልማትና አስተዳር ደንብ ቁጥር 163/2016 (የመሬት ይዞታ መብት ፈጠራ እና አገልግሎት አሰጣጥ ደንብ ቁጥር 163/2016) ለረጅም ጊዜ የማህበረሰብ ጥያቄ ይፈታል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረዉ ደንብ ነው።
የቀበሌ ቤት በሚገኝበት ይዞታ ውስጥ ከግንቦት 1988 ዓ.ም በኋላ ለተገነባ ቤት የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ አይሰጥም።
“ራሱን ችሎ የሚለማ መሬት” ማለት የቦታ ስፋቱ 75 ሜትር ካሬና በላይ ሆኖ 4 ሜትር ስፋት የመዳረሻ መንገድ ያለው ቦታ ነው።
የሚሉትን የያዘ ሲሆን ዘጠኝ ክፍሎች አሉት።
- ክፍል አንድ: ጠቅላላ ድንጋጌዎች
- ክፍል ሁለት: እስከ ግንቦት 1988 ዓ.ም ድረስ የተያዙ የሰነድ አልባ ይዞታዎች ካርታ አሰጣጥ
- ክፍል ሶስት: ለአምልኮ ማካሄጃ የዋሉ ይዞታዎች ካርታ አሰጣጥ
- ክፍል አራት: የይዞታ አገልግሎት አሰጣጥ
- ክፍል አምስት: የመረጃ አደረጃጀት፤ የይዞታ ማህደር አያያዝ እና የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ
- ክፍል ስድስት: የካርታ ይዘት
- ክፍል ሰባት: ካርታ ስለማገድና ስለማምከን
- ክፍል ስምንት: አግባብ ባለው አካል ሳይፈቀዱ ለተያዙ ይዞታዎች ካርታ አሰጣጥ
- ክፍል ዘጠኝ: ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
ሙሉ ደንቡ ከታች አያይዘናል።














