ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ዲጋ ወረዳ የገነባው የአርጆ ድንጋይ ከሰል ፋብሪካ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመረቀ፡፡
ፋብሪካው በሰዓት 200 ቶን ታጥቦ የደረቀና ደረጃውን የጠበቀ የድንጋይ ከሰል የማምረት አቅም አለው፡፡
በምርቃት ስነስርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ባልስልጣናት የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አሕመድ እና ጥሪ የተደረገላችው አንግዶች ተገኝተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ የአርጆ የደንጋይ ክሰል ፋብሪካ፤ ከውጭ ሲገባ የነበረውን የተፈጨ ድንጋይ ፍላጎት በሀገር ውስጥ በማሟላት በኢትዮጵያ የዘርፉ የኢንደስትሪ ልማት ዐቢይ ሚና ይጫወታል ብለዋል።
ፋብሪካው ለሲሚንቶ፣ ለብረት እና ኮንስትራክሽን ኢንደስትሪዎች አስፈላጊ ጥሬ ግብዓቶችን ያቀርባል። በተጨማሪም ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃን በማረጋገጥ የኢንደስትሪ ልማትን እንደምታሳድግ ማሳያ ነው ሲሉም አክለዋል፡፡
ምንጭ: AMN, ሚደሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ


















