በሀገራችንም አዋጅ ቁጥር 721/2004 በአንቀፅ 2(1) ላይ ሊዝ ማለት በጊዜ በተገደበ ውል መሰረት የከተማ ቦታ የመጠቀም መብት በውል የሚተላለፍበት ወይም የሚያዝበት የመሬት ይዞታ ስሪት ነው በማለት ደንግጓል፡፡
የሊዝ ዘመን:- ለመኖሪያ ቤት፣ ለሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ለምርምርና ጥናት፣ ለመንግስት መሥሪያ ቤት፣ ለበጎ አድራጎት ድርጅትና ለሃይማኖት ተቋም 99 ዓመታት ነው።
በከተማ መልሶ ማልማት ፕሮግራም ምክንያት ተነሺ የሚሆን የነባር ይዞታ ባለመብት ምትክ ቦታ የማግኘት መብት ይኖረዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ወይም የቀበሌ መኖሪያ ቤት ህጋዊ ተከራይ የሆነ ሰው በከተማው መልሶ ማልማት ፕሮግራም ምክንያት ተነሺ በሚሆንበት ጊዜ የጋራ መኖሪያ ቤት በግዥ የሚያገኝበት ሁኔታ ይመቻችለታል፡፡
የመንግስት ወይም የቀበሌ የንግድ ቤት ህጋዊ ተከራይ የሆነ ሰው በከተማ መልሶ ማልማት ፕሮግራም ምክንያት ተነሺ በሚሆንበት ጊዜ በሚመለከተው ክልል ወይም የከተማ አስተዳደር በሚወሰነው መሠረት ይስተናገዳል፡፡
አዋጁ 5 ክፍሎች አሉት
- ክፍል አንድ፡ ጠቅላላ ድንጋጌዎች
- ክፍል ሁለት፡ መሠረታዊ የሊዝ ድንጋጌዎች
- ክፍል ሦስት፡ የከተማ ቦታ ሊዝ አስተዳደር
- ክፍል አራት፡ የከተማ ቦታ ስለማስለቀቅ
- ክፍል አምስት፡ ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
ሙሉን የአዋጅ ቅጅ ከታች አያይዘናል።

















