የኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም ክንውን 95 ነጥብ 2 በመቶ እንደሆነም በሪፖርቱ ተመላክቷል።
በሩብ ዓመቱ ከ2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱም ተገልጿል።
ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከእጥፍ በላይ የገቢ እድገትም ተመዝግቧል።
ግምገማው በዋናነት በ 2018 በጀት ዓመት ኮርፖሬሽኑ ተግባራዊ የሚያደረጋቸውን ግዙፍ እቅዶችንና ፕሮጀክቶችን ለማሳካት በሩብ ዓመቱ የተከናወኑ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ።
በዚህም በተለይ እንደሀገር የግንባታ ዘርፉን ያለበትን የቴክኖሎጂ አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ የተከናወነው ሥራ፣ የአቅም ግንባታ ሥራዎችና የመፈጸም አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉ፣ የገቢ ማስገኛ ሥራዎች፣ ስትራቴጂክ ሥራዎች አተገባበር ውጤታማ እንደሆነ ተገምግሟል።
ቤት ከመገንባት ወደ ማምረት የሚያሸጋግረን የ3ዲ ኮንክሪት ፕሪንት ቴክኖሎጂን ኮርፖሬሽኑ ተግባራዊ ለማድረግ ከኦስትሪያው ኩባንያ በውሚት ጋር የተደረገው ስምምነት አፈፃፀሙ በጥሩ ጎኑ ተገምግሟል።
የቤት ልማት ዘርፉን የሚያሳድጉ የኮንስትራክሽንና የግብዓት ማቅረቢያ ተሸከርካሪዎች እና ማሽኖችን ወደ ሥራ መግባታቸው ገቢን ከማሳደግና የግንባታ አቅምን ከማጎልበት አኳያ ትልቅ ሚና እንዳለውም ተመላክቷል።
በሩብ ዓመቱ በግንባታ ተቋራጭነት፣ በሪኖቬሽን ሥራ፣ ከግብዓት ሽያጭ፣ ከመደበኛ የቤት ኪራይ፣ ከቤት ሽያጭ የተገኘው ገቢ ከፍተኛ እድገት መመዝገቡም ተጠቅሷል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመኖሪያ ቤት ፕሮጀክትን በተያዘለት ጊዜና ገደብ አጠናቆ ማሰረከብ መቻሉም በግምገማው ተነስቷል።
በተያዘው በጀት ዓመትም በታክስ ክፍያ የተገኘውን የኘላቲኒየም ደረጃ ለማስቀጠል እና የክፍያ መጠኑን ለማሳደግ እንደሚስራም ተገልጿል።
በፍ/ቤት ክርክር ከሕገ ወጦች የተመለሱ ይዞታዎች ብዛት በአሁኑ ሰዓት ከ58 በለይ መድራሳቸውንም በግምገማው ተጠቅሷል።
በቀጣይ የበጀት ወራት የሚከናወኑ ቀሪ ተግባራትን ለማካናወን የሚያስችል ዝርዝር የአፈፃፀም አቅጣጫ በማስቀመጥ ግምገማው ተጠናቋል።
ምንጭ፡ Federal Housing Corporation


















