ዩስራ ሆም (Yusira Home) በመዲናችን አዲስ አበባ የመጀመሪያውን Ashley Furniture Homestore በመክፈት ከዓለም አቀፍ የቤት ዕቃ ብራንዶች መካከል አንደኛ የሆነውን አሽሊ ፈርኒቸር ወደ ኢትዮጵያ ገበያ አስገብቷል።
በኢትዮጵያ የአሽሊ ፈርኒቸር ብቸኛ ወኪልና አቅራቢ የሆነው ዩስራ ሆም በመዲናችን ብስራተ ገብርኤል አካባቢ የመጀመርያ ማሳያ ቦታ በመክፈት የአሽሊ ፈርኒቸር ምርቶች ለኢትዮጵያዊያን አስተዋውቋል።
በመክፈቻዉ ስነ-ስርዓቱ ላይ የአሜሪካ አምባሳደር ለኢትዮጵያ ኤርቪን ማሲንጋ (Ervin Massinga)፣ የዩስራ ሆም መሥራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ ዩስራ ኑርሁሴን ረጃ፣ እንዲሁም የአሽሊ ፈርኒቸር የአለም አቀፍ ሽያጭ ምክትል ፕሬዚዳንት ከርት ሄንስ (Kurt Haines) ጨምሮ ዲፕሎማቶች፣ የንግድ መሪዎች፣ የሚዲያ ተወካዮች እና እንግዶች ተገኝተዋል።
አሽሊ ፈርኒቸር ኢንዱስትሪ ከ80 ዓመታት በላይ ልምድ፣ የላቀ የማምረት ችሎታ እና በ155 አገሮች ውስጥ ከ1100 በላይ ሱቆች ያሉት የዓለም ትልቁ የቤት እቃ አምራች ነዉ። በዩስራ ኑርሁሴን ረጃ የተመሰረተው ዩስራ ሆም በዚሁ ዘርፍ ጥራትና ውበት የተላበሱ የቤት ዕቃዎች ለገበያው እያቀረበ ይገኛል።
በመክፈቻው ላይ ንግግር ያደረጉት ዩስራ ኑርሁሴን ረጃ እንዲህ ብለዋል፡- “አሽሊ ፈርኒቸር ወደ ኢትዮጵያ መግባት አገሪቱ ለአለም አቀፍ ኢንቨስትመንት እያደረገች ያለችውን ክፍትነት እና የኢኮኖሚ ለውጡን ያንፀባርቃል።”
አዲሱ Ashley Furniture Homestore ሁሉም አይነት የቤት ፈርኒቸሮች ጨምሮ በአንድ ቦታ በማቅረብ ለኢትዮጵያውያን ዓለም አቀፍ ጥራት ያላቸው ምርቶች የሚያቀርብ ይሆናል።
ምንጭ: FastMereja


















