ሁለተኛው ዙር የመንግስት የንግድ ቤት ጨረታ አሽናፊዎች ውጤት ይፋ ተደረገ፡፡
ማስታወቂያ
የሁለተኛ ዙር የንግድ ቤት ኪራይ ጨረታ ውጤት ይፋ ስለማድረግ፤የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ በከተማው በተለያዩ አካባቢዎች በጋራ መኖሪያ ህንፃ ላይ እና የኮሪደር ልማት በተሰራባቸው አካባቢዎች የሚገኙ የመንግስት ንግድ ቤቶችን በጨረታ አወዳድሮ በኪራይ ለማስተላለፍ ከመስከረም 22 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ግልፅ ጨረታ ፍላጎት ላላቸው ተወዳዳሪዎች ክፍት በማድረግ ከጥቅምት 18/2018 እስከ ጥቅምት 20/2018 ድረስ ተጫራቾች በተገኙበት ጨረታው የተከፈተ መሆኑ ይታወቃል፡፡
በዚህም መሰረት የጨረታው ውጤት ተጠናቅሮ የተጠቃለለ በመሆኑ የሁለተኛ ዙር የመንግስት ንግድ ቤቶች ጨረታ ውጤት በዚህ ማስታወቂያ ይፋ የተደረገ መሆኑን እየገለፅን ተወዳዳሪዎች ከዚህ በታች በተያያዘው ሰንጠረዥ ውጤቱን እንድታዩ እናሳውቃለን፡፡
በውጤቱ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተጫራቾች የጨረታ ውጤቱ በጋዜጣ፣ በቢሮው ይፋዊ የቴሌግራም እና ፌስቡክ ገፆች ይፋ ከተደረገበት ጥቅምት 22 ቀን 2018 ጀምሮ እስከ ጥቅምት 29 ቀን 2018 ድረስ (ቅዳሜ ግማሽ ቀን ጨምሮ) ቅሬታችሁን በአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ 12ኛ ፎቅ ለቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን የጨረታ አሸናፊዎች ከህዳር 04 ቀን 2018 ጀምሮ ባሉት 10(አስር) ተከታታይ የሥራ ቀናት ንግድ ቤቱ የሚገኝበት ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ ውል እንድፈፅሙ እናሳስባለን፡፡
አሽናፊዎች ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች መመልከት ትችላላችሁ፡፡
ምንጭ፡ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ


















