ግብር የሚከፈልበት የኪራይ ገቢ የሚባለው በግብር ዓመቱ ግብር ከፋዩ ቤት በማከራየት ካገኘው ጠቅላላ ዓመታዊ ገቢ ላይ ለግብር ከፋዩ የተፈቀደው ጠቅላላ ወጪ ተቀናሽ ተደርጎ የሚቀረው ገቢ ላይ ነው፡፡
ግብር የሚከፈልበት የቤት ኪራይ ገቢን በተመለከተ ቤት ወይም ህንጻ በማከራየት የሚገኝ ጠቅላላ ገቢ የሚከተሉትን ይጨምራል፡-
- የኪራይ ዋጋ ጭማሪን ወይም ተመሳሳይ ክፍያዎችን ጨምሮ በኪራይ ወሉ መሠረት ግብር ከፋዩ በግብር ዓመቱ የሚያገኘው ማናቸውም የገንዘብ መጠን፣
- በኪራይ ውሉ መሠረት ተከራይ አከራዩን በመወከል በግብር ዓመቱ ለሌሎች የሚከፍላቸው ክፍያዎች፣
- በቤቱ ላይ ለሚደርሰው ጉዳት ማስተካከያ ይሆን ዘንድ ግብር ከፋዩ የያዘውና በግብር ዓመቱ ያልተጠቀመበት ለግብር ከፋዩ ገቢ የተደረገው ማናቸውም ቦንድ፣ ዋስትና ወይም ተመሳሳይ የገንዘብ መጠን፣
- ለግብር ከፋዩ ከሚከፈለው ኪራይ በተጨማሪ በኪራይ ውል መሠረት ተከራይ ራሱ ለቤቱ እድሳት ወይም ማሻሻያ የሚያወጣው ገንዘብ፣
- ግብር ከፋዩ ቤቱን ያከራየው ከዕቃዎች ጋር በሚሆንበት ጊዜ ያገኘው ጠቅላላ ገቢ ከዕቃዎቹ የተገኘውን የኪራይ ገቢም ያጠቃልላል፡፡
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥርና አስተዳደር አዋጅ ጸደቀ

የተከራይ አከራዮች
- የተከራይ አከራይ በግብር ዓመቱ ያገኘው ግብር የሚከፈልበት ገቢ ነው የሚባለው የተከራይ አከራይ በግብር ዓመቱ ከተቀበለው ጠቅላላ የኪራይ ገቢ ላይ ለዋናው አከራይ የሚከፍለው ኪራይ እንዲሁም ገቢውን ለማግኘት ያወጣቸው ሌሎች ወጪዎች ከተቀነሱ በኋላ የሚቀረው ገንዘብ ነው፡፡
- ተከራይ የተከራየውን ቤት መልሶ እንዲያከራይ የሚፈቅድ የቤት ባለቤት ተከራዩ ግብሩን ሳይከፍል ቢቀር ስለእርሱ ሆኖ ግብሩን የመክፈል ኃላፊነት ይኖርበታል፡፡

















