ከአዲስ አበባ 136 ኪ.ሜ ቅርብ ርቀት ላይ በ5 ቢሊዮን ብር እየተገነባ የሚገኘው በሱፍቃድ ሪል እስቴት ለወረዳ ከተሞች ልማት ስትራቴጂ ስኬት ግዙፍ ዐቅም እየሆነ ነው።
ከተመሰረተ ገና የሁለት ዓመታት ዕድሜ ያለውና በአማራ ክልል በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አረርቲ ከተማ እየተገነባ ያለው በሱፍቃድ ሪል እስቴት የቤት ፈላጊዎችን ምርጫ ያሟላና ዘመናዊ መንደር እየፈጠረ ይገኛል።
ከዋና ዋና ከተሞች ወጣ ብሎ ወረዳዎችንና አዳጊ ከተሞችን በማነቃቃት፣ የኢንዱስትሪ ልማት ፍሰቶቻቸውን የሚያግዝ፣ የማኅበረሰቡን አኗኗር (Housing Lifestyle) በማዘመን የከተማ ልማት እያፋጠኑ ከሚገኙ ጥቂት ፕሮጀክቶች ቀዳሚ ነው።
ይህ በሰሜን ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አረርቲ ከተማ እየተገነባ ያለው አዲስ የመኖሪያ መንደር ለቤት ደንበኞቹ አስተማማኝ የቤት ግንባታ አገልግሎት እና የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያገኙ በማድረግ አሳታፊ የከተማ ልማት ፍልስፍና ይከተላል።

የበሱፍቃድ ሪል እስቴት ልማት ኩባንያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የምንጃር ሸንኮራዋ አረርቲ ከተማ ስትጠራ ስሙ አብሮ የሚነሳው በሱፍቃድ ሪል እስቴት በ230,000 ካሬ ሜትር ላይ እየተገነባ ያለው ግዙፍ የመኖሪያ መንደር 1,000 ቤቶችን፣ ባለ 5 ኮኮብ ሆቴል፣ ከአጸደ-ሕጻናት እስከ ኮሌጅ ድረስ ደረጃውን የጠበቀ የትምህርት ተቋም እና የጤና ተቋማት፣ ለስምጥ ሸለቆዋ የቱሪስት መዳረሻ አረርቲ ተስማሚ የመዝናኛ ስፍራዎችን ያካተተ አዲስ መንደር እየገነባ ነው።
የበሱፍቃድ ሪል እስቴት ቅዳሜ ግንቦት 02 ቀን 2017 ዓ.ም የግንባታውን ሂደትና አጠቃላይ የሥራውን እንቅስቃሴ አስመልክቶ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም ደምበኞች በተገኙበት የሳይት ጉብኝት ያደረገ ሲሆን ለሠላሳ አምስት ደንበኛች ደግሞ የካርታና የይዞታ ማረጋገጫ ርክክብ አከናውኗል።
ምንጭ፡ ማናዬ እውነቱ


















