ቺባን ሪል ስቴት የቺባን ፕሮፐርቲስ እሕት ኩባንያ የሆነው “አልፋ ባለ አምስት ኮከብ ሌግዠሪ መኖሪያ አፓርትመንት” ፕሮጀክቱን አዲስ አበባ፣ 22 አካባቢ መርቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉን አስታወቀ።
ከመኖሪያ ቤቶቹ ውጭ ያሉት አገልግሎት መስጫ ህንጻዎች የግንባታ ሂደት ደግሞ 80 በመቶ መድረሱ ነው የተነገረው፡፡
ፕሮጀክቱ በመጀመሪያ ከታቀደለት የሁለት ዓመት ተኩል የግንባታ ጊዜ ቀደም ብሎ ከአንድ ዓመት እስከ አንድ ዓመት ተኩል ባለው ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለገዢዎች እንደሚተላለፍ የግንባታው አስተባባሪዎች ገልጸዋል።
ፕሮጀክቱ የመኖሪያ ቤት አገልግሎትን ከከፍተኛ የሆቴል ምቾት ጋር ያጣመረ ሲሆን፥ ባለ 17 ወለል ፕላን ያለው ሆኖ ስቱዲዮን ጨምሮ እስከ ሶስት የመኝታ ክፍል አማራጮች አሉት።
የሆቴል ሎቢ፣ ሬስቶራንት፣ ካፌ፣ ጂም፣ የመዋኛ ገንዳ እና የልጆች መጫወቻ ስፍራዎችን ግንባታው አካቷል፡፡ በተጨማሪም፣ ሁለት ሰፋፊ ፔንት ሃውሶችንና አንድ የራሱ መዋኛ ያለው ባለሁለት ወለል እጅግ ቅንጡ ፔንት ሀውስ ይዟል።
እንዲሁም ዕንግዶች እና ነዋሪዎች የሚጠቀሙበት ቅንጡ ሎቢ እና የሪሴፕሽን ቦታን በግራውንድ ፍሎር ላይ ያካተተ ሲሆን፣ በዚህ ኢንቨስትመንት ላይ በአጋርነት ለመሳተፍ ለሚፈልጉ ደንበኞች ደግሞ የተረጋገጠ አስራ ሰባት ከመቶ ዓመታዊ ገቢ የሚያስገኝ ዕድል የተመቻቸ መሆኑ ተብራርቷል።
ነዋሪዎች ወደ ቤታቸው የሚገቡት በዘመናዊ የካርድ አጠቃቀም ዘዴ (Card Access) ሲሆን፣ ይህም ከፍተኛ ደሕንነትን እንዲሰማቸው ያደርጋል ያለው ቺባን ፕሮፐርቲስ ነው፡፡
ምንጭ: DireTube, , EthioTimes


















