ኪ ሃውሲንግ ፋይናንስ ሶሉሽን በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ሃና ማሪያም ፍሬንድሺፕ ስቶር ፊትለፊት ባለ 15 ወለል ህንፃ አጠናቆ ለ150 ለዕድለኞች በዛሬው ዕለት አስተላልፏል።
ኪ ሃውሲንግ ፋይናንስ ሶሉሽን በአነስተኛ የገቢ ደረጃ የሚገኙ እና በተለመደው መንገድ የቤት ባለቤት መሆን ለማይችሉት የህብረተሰብ ክፍሎች በአነስተኛ ቅድመ-ክፍያ እና ከ 2ሺህ ብር በሚጀምር ዝቅተኛ ወርሃዊ ቁጠባ የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ለማስቻል እየሰራ እንደሚገኝ ተነግሯል።
ድርጅቱ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ስድስት (6) ሳይቶች እና በባህር ዳር ከተማ በሁለት (2) ሳይቶች ዕድለኞችን የቤት ባለቤት ማድረጉን ተገልጿል።
ምንጭ: FastMereja


















