Hybrid Designs(ራይድ) ትራንስፖርት አገልግሎት በቅርቡ ባስጀመረው የሎተሪ መርሃ ግብር አሸናፊ ለሆኑ ደንበኞች የመኖሪያ ቤት ሽልማትን አበርክቷል።
የራይድ መስራች እና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሳምራዊት ፍቅሩ በዝግጅቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ድርጀቱ እንዲህ ዓይነት የሎተሪ መርሃ ግብሮችን የሚያዘጋጀው የደንበኞቹን ሕይወት በተሻለ መልኩ ለመቀየር ካለው ራዕይ በመነሳት መሆኑን ገልፀዋል።
“ራይድ ማንኛውንም ዓይነት ኢኒሼቲቭ ይዞ ሲመጣ የሰውን ሕይወት መቀየር አለበት ብለን እናምናለን” ያሉት ሥራ አስኪያጇ የሎተሪው ዋና ዓላማም የአሸናፊዎችን የቤት ኪራይ እና መሰል ወጪዎችን በማቃለል ደንበኞቻችን የተረጋጋ ሕይወት እንዲመሩ ማስቻል መሆኑንም አስረድተዋል።
በመርሃ ግብሩ የቤት ባለቤት የሆኑት ወይዘሮ ሕይወት ደበላ ለሽልማት ያበቃቸውን የመኖሪያ ቤት ቁልፍ ተረክበዋል። የመኖሪያ ቤት አሸናፊዋ ከሶስትና ከአራት ዓመታት በላይ የራይድ ትራንስፖርት ደንበኛ እንደነበሩ ጠቅሰዋል። በሁለተኛ ደረጃ በOvid Real Estate በተገነባው በ4 ኪሎ ጥይት ቤት በሚገኘው አፓርትመንት የቤት ተሸላሚ ሆናለች።
ድርጅቱ ይህ የሽልማት መርሃ-ግብር በዚህ እንደማያበቃ እና ወደፊትም በሌሎች የተሻሉ ዝግጅቶች እንደሚቀጥል አስታውቋል።
ራይድ በቀጣይ የሚኖሩትን እንደዚህ ዓይነት አበረታች ዝግጅቶች እንዲሁም የሚቆዩበትን ጊዜና የሽልማት ዓይነቶችን በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግም ዋና ሥራ አስፈፃሚዋ አስታውሰዋል።
ምንጭ: FastMereja.com


















